>

Friday, 14 November 2014

መልክ የሌለው ውብ፣ ጣዕም የሌለው ጥዑም



አንዳንድ ጊዜ ሁሉን ነገር በትኩረት ለመመልከት ሞክሩ በተለይ አምላካችን እግዚአብሔር የፈጠራቸው ፍጥረታትን በአንክሮ ብትመለከቷቸው መልካም ነው፤ ምክንያቱም ከልባችሁ እየተቀበለ አፋችሁ የሚናገራቸው ውድ ቃላት ሊገልጡት የማይቻላቸው ውበት አላቸውና፡፡ የሥነ ፍጥረትን ነገር አስብና በሰማይና በምድር የሞላውን ፍጥረት እመለከትና መገረም ይይዘኛል፤ አባ ሕርያቆስ በቅዳሴው ‹‹የፍጥረታትን አነዋወራቸውን፣ የሰማይን ምጥቀቱን፣ የምድርን ስፋቱን ሊያይ ህሊናየ በነፋሳት ትከሻ ላይ ሆኖ ምሥራቅና ምዕራብን፣ ሰሜንና ደቡብን ይበራል ነገር ግን የሥነ ፍጥረት አኗኗር አልመረመረው ብሎ ህሊናዬ ወደ አለመመርመር ይመለሳል›› ብሎ የተናገረው የሥነ ፍጥረት ጉዳይ አስደናቂ መሆኑን ለመግለጥ ነው፡፡ 
የትኛዉም ዐይነት ፍጥረት ያለ አንዳች ፍጥረት እንዳልተፈጠረ እርግጠኛ ሆኘ እነግራችሁ አለሁ፤ ቢሆንም ግን የአንዱ ውበት ከሌላው የተለየ መሆኑ ደግሞ የበለጠ እንድንደነቅ የሚያደርገን ሲሆን ምድራዊውን ኑሯችንን እንዳይሰለችና ምቾት ያለው እንዲሆን ያደረገልን ይህ የሥነ ፍጥረት ውበት እንደሆነ አስባለሁ፡፡
ለማንኛውም