>

Saturday, 18 June 2016

አዲሱን መሥዋዕት ለእግዚአብሔር


እስራኤል የሚያከብሯቸው ዘጠኝ ያክል በዓላት ያሏቸው ሲሆን በተለየ ሁኔታ ሦስት ዐበይት በዓላት አሉ፤ እነርሱም፡- በዓለ መፀለት፣ በዓለ ፍሥሕ እና በዓለ ሰዊት፤ ናቸው ዛሬ ማየት ምፈልገው በዓለ ሰዊትን ነው፤ይህ በዓል ፋሲካን ካከበሩ በኋላ በሃምሳኛው ቀን እንዲያከብሩት የታዘዘ በዓል ነው ‹‹ከሰንበት ማግስት ፍፁም ሰባት ሱባዔ ቁጠሩ እስከ መጨረሻ ሰባተኛ ሰንበት ማግሥት ድረስ አምሳ ቀን ቁጠሩ አዲሱንም መሥዋዕት ለእግዚአብሔር አቅርቡ›› ዘሌ 23÷16 አዲስ መሥዋዕት ያቀርቡባት ዘንድ የተዘጋጀች አዲስ ቀን ናት ባለፈው በዓለ ፍሥሕን ሲያከብሩ ‹‹እንጀራውንም የተጠበሰውንም እሸት ለምለሙንም እሸት የአምላካችሁን መሥዋዕት እስከምታቀርቡበት እስከዚህ ቀን ድረስ አትብሉ›› ዘሌ 23÷14 ተብለው መታዘዛቸውን እናስታውሳለን፡፡
ከስሙም እንደምንረዳው በዓለ ሰዊት ማለት የእሸት በዓል ማለት ነው፤ አዲሱ እህል ሲደርስ የምድሩን ፍሬ ቀዳምያት ለእግዚአብሔር የሚያስረክቡበት ቀን ነው ዓለም የሚድነው በቀዳማዊ ቃል ነውና ቀዳምያቱ ለእግዚአብሔር ይገባ ነበር፤ ቀዳማዊ ቃል ሥጋን ለብሶ እስኪመጣ እና ቀዳማዊ ቃል የተዋሐደውን ሥጋ መሥዋዕት አድርገን በፊቱ እስክናቀርብ ድረስ ሌላ ምን ይዘን ልንቀርብ እንችላለን፤

Thursday, 9 June 2016

እርገት

የዛሬው እርገት በሥጋ የተደረገ እርገት እንጅ እግዚአብሔር በባሕርዩ ከዚህ ያለ ከዚያ የሌለ ሆኖ ከዚህ ወደዚያ ሄደ ማለታችን አይደለም፤ ሰው በሆነ ጊዜ ከሰማየ ሰማያት ወረደ ማለታችን ከዚህ የሌለ በዚያ ብቻ ያለ ነው ማለታችን ሳይሆን ምድራዊነትን ገንዘብ አደረገ ማለታችን እንደሆነ ሁሉ አሁንም ወደ ሰማይ ወጣ ስንል በሥጋ ግብር መናገራችን መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ በእርግጥ ልንረሳው እማይገባ ዋናው ነገር የሥጋ እርገት የቃል ርደት የተፈጸመው በማኅፀነ ማርያም መሆኑን ነው ለዚህ ነው ሊቁ አባ ሕርያቆስ እመቤታችንን ባመሰገነበት ድርሳኑ ‹‹ ምዕራግ እምድር እስከ ሰማይ፤ ከምድር ወደ ሰማይ መውጫ መሰላል ሆይ..›› ብሎ ማመስገኑ፡፡ ጌታችንም ከእርገት አስቀድሞ በመዋዕለ ስብከቱ ‹‹አልቦ ዘዐርገ ውስተ ሰማይ ዘእንበለ ዘወረደ እምሰማይ፤ ከሰማይ ከወረደው በቀር ወደ ሰማይ የወጣ ማንም የለም›› ዮሐ 3÷13 ብሎ ያስተማረው እርገት በማኅፀነ ማርያም ስለተፈፀመ ነው፡፡ ታዲያ እንዲህ ከሆነ የዛሬው እርገት ምንድነው? ብሎ የሚጠይቅ ቢኖር