>

Thursday, 18 August 2016



ሙሴና ኤልያስ በደብረ ታቦር
ደብረ ታቦር ከደብረ ሲና የሚበልጠውን ምሥጢር ያየንበት ተራራ ነው፤ በደብረ ሲና በሁለቱ ጽላት ላይ የተጻፉ ቃላትን ተቀብለናል፤ በደብር ታቦር ግን አካላዊ ቃል ተገልጦ ታየልን፤ በደብረ ሲና ሙሴ ብቻውን ቆሞ ነበር በደብረ ታቦር ግን ነቢያት ከሐዋርያት አንድ ሆነው ተስማምተው ክርስቶስን መካከል አድርገው ታዩ፡፡ እነዚህ ሁለቱን ከነቢያት ለይቶ ለምን ይጠራቸዋል፤ ከነሱ በላይ የሚጠራቸው አብርሃም ይስሐቅ ያዕቆብ ያሉ አይደለምን! ሙሴና ኤልያስ ለምን ለዚህ ምሥጢር የተለዩ ሆኑ?
ቅዱስ ወንጌል ‹‹ወናሁ አስተርአዩ ሙሴ ወኤልያስ እንዘ ይትናገሩ ምስሌሁ፤ እነሆ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር እየተነጋገሩ ታዩ›› ማቴ 17÷4 ብሎ በስም የጠራቸው እነዚህ ነቢያት ከብሉይ ኪዳን ነቢያት ሁሉ የሚያመሳስላቸው ታሪክ ያላቸው ነቢያት ናቸው፤

Wednesday, 10 August 2016

ሱባኤ



ሱባኤ
·        ---- --------------- የሱባኤ ጥቅሙ ምንድነው?
·      , ------------   ------እመቤታችን የሞተችው በጥር ከሆነ ሐዋርያት እስከ ነሐሴ ሱባኤ ያልገቡት ለምነድነው?
·         ---------------ትንሣኤዋ በሦስተኛው ሱባኤ ተገለጠላቸው ሱባኤውን ያልጨረሱት ለምንድነው?
--------እነዚህን እና ሌሎችን ጥያቄዎችን በዚህ ጽሑፍ ለመመለስ እንሞክራለን
ነገር ሁሉ ከእግዚአብሔር እንዲደረግልን ስንሻ ሱባኤ መግባት በአባቶቻችን ሕይወት የተማርነው የጥያቄ ማቅረቢያ መንገድ ነው፤ በሱባኤ ምሥጢር ይገለጣል፤ በሱባኤ በረከት ይገኛል፤ በሱባኤ ዕጣ ፋንታን ማስተካከል ይቻላል፤ ሁሉም በጎ ነገሮች የሱባኤ ውጤቶች ናቸው፤ የሔዋን መፈጠር በሱባኤ ነው የእስራኤል ከፋርስ ባቢሎን መውጣት በሱባኤ ነው፤ የክርስቶስ ልደት በአበው ሱባኤ ነው፤ የሰው ልጆች ከሲኦል መውጣት በሱባኤ ነው፤ በመጨረሻም የታላቁ ዓለም የመንግሥተ ሰማያት መምጣት በሱባኤ ነው፤